You are here: HomeSocial Issues ዓለም ሁሉ ጦር ሜዳ ሆኗልና እንግዲህ ንቁ!

ዓለም ሁሉ ጦር ሜዳ ሆኗልና እንግዲህ ንቁ!

Written by  Tuesday, 06 May 2014 00:00
Mamusha Fenta Mamusha Fenta

በእኔ አመለካከት ትርጉማቸዉ በፍጥነት እየተቀየሩ ከመጡ ሃሳቦች መካከል አንዱ “የጦር ሜዳ” የሚለዉ ነው። ቃሉ ለዘመናት ያገለገለዉ ከሰላማዊ ሰዎች መኖሪያ ወጣ ተብሎ ለጦርነት የሚያገለግልን ሥፍራ ለማመልከት ነዉ። የጥንት ጦርነቶች ከከተማ ቅጥሮች ዉጪ ተካሂደዉ፤ ያሸነፈዉ አካል ለምርኮና ለብዝበዛ ወደ ከተሞች ዘልቆ ይገባ ስለነበር ጦርነቶቹ የሚካሄዱበት የተለየዉ ሥፍራ ነበር “የጦር ሜዳ” የሚባለዉ። አጠቃላይ ትርጉሙንና ልምዱን ለማሳየት እንጂ ከዚህ በተለየ መልኩ ሰላማዊ ሰዎችን ኢላማ ያደረጉ ዘግናኝ ጦርነቶችም በሰዉ ልጅ ታሪክ ዉስጥ ነበሩ።

 

በአጠቃላይ ግን “ጦር ሜዳ የሚሄድ ዘማች” እና “በቤት የሚቀር/በሰላማዊ ቦታ የዘወትር ተግባሩን የሚያከናዉን ዜጋ” የተለያዩ ነበሩ። አሁን እንዲህ ያለ ነገር መቅረቱን በግልጽ እናስተዉላለን። ዓለም በሞላ የጦር ሜዳ ሆናለች። ያለንበት ማንኛዉም ቦታ (የሥራ፣ የገበያ፣ የመዝናኛ ወ.ዘ.ተ.) በቅጽበት ወደ ጦር ሜዳነት ሊቀየር ይችላል። በጥቂት ቀናት ልዩነት የዋሽንግተን የባህር ኃይል መሥሪያ ቤትና የአሁኑ የጎረቤታችን ናይሮቢና ናይጄሪያ ዘግናኝ እልቂቶች ይህንን ያመላክቱናል። ሰዎች በጠዋት ተነስተዉ ወደ ሥራ፣ገበያ፣ መዝናኛ እንጂ ወደ “ጦር ሜዳ” መሄዳቸዉን አላስተዋሉም። በነገራችን ላይ፣ ሰሞኑን እየታየ ባለዉ “ፊልም መሳይ” የሰላማዉያን እልቂት የተሰማኝ ሃዘንና የጸሎት ሸክም በቃሌ ልገልጸዉ አልችልም።

 

ታዲያ እንዲህ ባለ ዘመን:-

አንደኛ ስለእያንዳንዷ ቀን የሕይወት ስጦታ፤ የሕይወታችንን ባለቤት እንድናመሰግን ሊያደርገን ይገባል። ሕይወትን እንደዘበትና እንደሚገባን ነገር አንቁጠር። በጦር ሜዳ ዓለም የተሰጠንልዩ ጸጋ በመሆኑ ማመስገን ይገባል።

 

በሌላ በኩል ደግሞ የጌታችን ኢየሱስን ቃል ሊያስታዉሰን ይገባል (ማቴ 24፡6 7)። ጦርና የጦር ወሬ የመምጣቱ አንድ አመልካች አስታዋሽ/ደወል በመሆኑ ነቅቶ መኖርና መጠበቅ ይገባል። “አትደንግጡ” ያለንን ጌታ ታምነን በእምነት “በሞት ጥላ መካከል እንኳን ብሄድ፣ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም” እንላለን። በተጨማሪም ለዘብተኛ መንፈሳዊነትን፣ ማፈግፈግን፣ መንፈሳዊ እንቅልፍን አስወግደን በትጋት ከጌታ ጋር እለት እለት መራመድ ግድ ነዉ። We can not afford to be weak or to backslide! በመጨረሻም ክርስቶስን በግል በማመንና በመከተል መዳን ያስፈልገናል። ጌታን ስናምን ሞት አያስፈራንም፤ ምክንያቱም ከሁለተኛዉ ሞት (ከገሃነም) የተረፍን በመሆኑ። “ሞት ሆይ መዉጊያህ የት አለ” (1ቆሮ 15፡54) በሚል የትንሣኤ እምነት እንመላለሳለን።

በአጠቃላይ የዛሬዉ ምክሬ ይህ ነዉ፡-

ዓለም ሁሉ ጦር ሜዳ ሆኗልና እንግዲህ ንቁ!

Read 26740 times Last modified on Monday, 25 July 2016 08:05
Dr. Mamusha Fenta

Mamusha Fenta is a Bible expositor and conference speaker residing in Addis Ababa, Ethiopia.

Studied at

Website: mamushafenta.com Email This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

Nahu's Corner

 

 

 

.

Right Now

We have 223 guests and no members online

About Us

Semayawi Thought is an online magazine published in Amharic and English, focused on contents to spiritual and personal growth.